የአባላቱን የቁጠባና የብድር ባህል ማዳበር
ለአባላቱ ተስማሚና ተደራሽ የሆኑ የፋይናንስ አገልግሎት ማቅረብ
የጥሬ ገንዘብ አቅርቦት እጥረትን መፍታት
ማህበሩ ራስ አገዝ ባህሪን እንዲላበስ ማድረግ
የአባላትን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ
በማኅበራዊ ጉዳዮች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ፤
የአባላትን ኢኮኖሚ ችግሮች በተባበረ ጥረት መከላከል፣ መቋቋም እና ማስወገድ፤
አባላት ገንዘባቸውን አዋጪ በሆነ ዘርፍ እንዲያውሉ ምክር መስጠት ፤
የኢንቨስትመንት አቅምን በማሳደግ ጠንካራ የፋይናንስ ተቐም መገንባት
ስለ ነፅብራቅ
ነፀብራቅኃ/የተ/ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ.የተ.ኅ.ሥ ማህበር በአዋጅ ቁጥር 985/09 መሰረት ጥር 22/05/2014 ዓ.ም በ300 መስራች አባላት፣በ 1.5 ሚሊየን ብር ካፒታል ሲመሰረት አሁን ላይ 1290 በላይ አባላት ያለው እንዲሁም 18 ሚሊየን ብር ባላይ ካፒታል ያስመዘገበ የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ተደራሽ ያላደረጉትን የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማገልገልና የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከሶማሌ ክልላዊ መንግስት ኅብረት ሥራ ማህበራት ማደራጃ ማስፋፊያ ኤጀንሲ ፍቃድ የተሰጠውና በጅግጅጋ ከተማ የተመሰረተ ኃ.የተ.ኅ.ሥ ማኅበር ነው፡፡
ራዕያችን ከቁጠባ እና ብድር ተቋም በላይ የማህበረሰባችንን ህይወት ለመለወጥ እና ከፍ ለማድረግ ነው፡፡ የለውጡ አካል ይሁኑ፡፡ ዛሬ ይቀላቀሉን!